የሕይወት ትርጉም ምንድ ነው? በሕይወቴ ውስጥ ምን ባደርግ ነው ዓላማ፣ ስኬትና እርካታ የማገኘው። ዘላቂ ውጤት ያለው ሥራ ለማከናወን አቅሙ ይኖረኝ ይሆን? ብዙ ሰዎች ስለዚህ ጉዳይ ጥያቄ ማንሳታቸው አይቀርም። በሕይወታቸው ለማሳካት ያሰቡትን ጉዳይ ቢፈፅሙም ከአመታት በኋላ መለስ ብለው ከሰዎች ጋር የነበራቸው ግንኙነት እንዴት እንደተበላሸና ባዶነት ለምን እንደሚሰማቸው ሳይገርማቸው አይቀርም። አንድ የቤዝ ቦል ተጫዋች በዘርፉ ከፍተኛ ዝና ከተቀዳጀ በኋላ ጨዋታ ሲጀምር ሰዎች ምን ብለው ቢነግሩት ይመርጥ እንደነበር ቢጠይቁት “ከፍተኛ ደረጃ ከተደረሰ በኋላ ምንም እንደሌለ ቢነግሩኝ እመርጥ ነበር” ሲል በቁጭት ተናግሯል።
ብዙ ግቦች ባዶነታቸው የሚረጋገጠው እነሱን ለማከናወን በርካታ ዓመታት ካለፈ በኋላ ነው። በኛ ሰብዓዊ ሕብረተሰብ ትርጉም እናገኛለን ብለው በማሰብ ብዙ ሰዎች በርካታ ዓላማዎችን ያራምዳሉ። ከነዚህም የሕይወት ዓላማዎች የንግድ ስኬት፣ ሐብት፣ መልካም ግንኙነት፣ ወሲብ፣ መዝናናትና ለሌሎች ሰዎች ጥሩ ነገር መስራትን ያካትታሉ። ሰዎች ሲመሰክሩ እንደተስተዋለው ሐብት የማከማቸት፣ መልካም ግንኙነት የመመስረትና ደስታን የማግኘት ዓላማቸውን ቢያሳኩም ማንም ሊሞላው የማይችል ባዶነት እንደሚሰማቸው ተናግረዋል።
የመፅሐፈ መክብብ ፀሐፊ ይህንን ስሜት ለመግለፅ “ከንቱ!...የከንቱ ከንቱ! ሁሉ ከንቱ ነው” ይላል(መፅሐፈ መክብብ 1፡2)። የመፅሐፈ መክብብ ፀሐፊ የሆነው ንጉሥ ሰለሞን ከልክ በላይ የሆነ ሐብት፣ በእርሱ ዘመንና በኛ ጊዜ ከነበረ ማንም ሰው የሚበልጥ ጥበብ፣ በብዙ መቶ የሚቆጠሩ ዕቁባቶች፣ መንግስታት የሚቀኑበት ቤተመንግስትና የአትክልት ስፍራ፣ ምርጥ የሆነ ምግብ፣ ወይንጠጅና አለየተባለ መደሰቻና መዝናኛ ነበረው። ጠቢቡ አንድ ጊዜ ሲናገር ልቡ የተመኘውን ያሳድድ ነበር። በዓይኖቻችን የምናየውና በስሜቶቻችን የምናጣጥመው ኑሮ ብለን የምንኖረው “ከፀሐይ በታች ያለው ሕይወት” ከንቱ ነው ሲል አጣጥሎታል።
ይህ ባዶነት ለምን ተከሰተ? ምክንያቱም እግዚሐብሔር የፈጠረን የዚህና አሁን ከምንለማመደው ባሻገር ላለው ነገር ነው። ሠለሞን ስለእግዚሐብሔር ሲናገር “ሰው መርምሮ እንዳያገኝ ዘላለምነትን በልቡ ሰጠው” ብሏል። (መፅሐፈ መክብብ 3፡11)። ሁላችንም በልባችን እንደምናውቀው ያለው ነገር “እዚህና አሁን” ያለው ብቻ እንዳልሆነ እንገነዘባለን። የመፅሐፍ ቅዱስ የመጀመሪያ መፅሐፍ በሆነው በዘፍጥረት ውስጥ እግዚሐብሔር የሰው ልጅን በራሱ መልክ እንደሰራው እናነባለን። (ዘፍጥረት 1፡26)። እኛ ከሌላ ነገር (ከሌላ የሕይወት ቅርፅ) ይልቅ አፈጣጠራችን ወደ እግዚሐብሔር የቀረበ እንደሆነ የሚያሳየን ነው። ከዚህም በተጨማሪ የምናገኘው ነገር የሰው ልጅ በኃጢት ወድቆ የኃጢያት መርገም በምድር ላይ ከመምጣቱ በፊት የሚከተሉት ነገሮች ተግባራዊ ሆነዋል። (1) እግዚሐብሔር ሰውን ማህበራዊ ፍጡር አድርጎ አበጀው።(ዘፍጥረት 2፡ 18-25)፣ (2) እግዚሐብሔር ለሰው ልጅ ሥራ ሰጠው። (ዘፍጥረት 2፡ 15)፣ (3)እግዚሐብሔር ከሰው ጋር ህብረት ነበረው። (ዘፍጥረት 3፡ 8) እና (4) ሰው ምድርን እንዲገዛ እግዚሐብሔር ሥልጣን ሰጠው። (ዘፍጥረት 1፡ 26)። የእነዚህ ነገሮች ትርጉም ምንድ ነው? እነዚህ እያንዳንዱ ለሕይወታችን እርካታ እንዲያስገኙልን ነው። እግዚሐብሔር አቅዶ የነበረው፣ ነገር ግን እነዚህ ሁሉ (በተለይም ሰው ከእግዚሐብሔር ጋር ያለው ህብረት) ተለዋውጠዋል። ምክንያቱም የሰው ልጅ በኃጢያት ከወደቀ በኋላ እርግማን በምድር ላይ ተግባራዊ በመሆኑ ነው። (ዘፍጥረት 3)።
የመፅሐፍ ቅዱስ የመጨረሻ ክፍል በሆነው በራዕይ መፅሐፍ እግዚሐብሔር አንድ ነገር አስቀምጧል። አሁን በተጨማጭ የምናውቃቸውን ምድርና ሰማይን አስወግዶ አዲስ ምድርና ሰማይን በመፍጠር ዘላለማዊ ሕይወትን ይተካል። በዚያን ጊዜ ከዳነው የሰው ልጅ ጋር ሙሉ ህብረት ያደርጋል። ያልዳኑትን ይፈርድባቸውና እርባናየለሽ ተብለው ወደ እሳትባህር ይጣላሉ። (ራዕይ 20፡ 11-15)። የኃጢያት መርገም ይወገዳል። ከዚህ በኋላ ኃጢያት፣ ሐዘን፣ በሽታ፣ ሞትና ስቃይ ከቶ አይኖርም።( ራዕይ 21፡ 4)። አማኞችም ሁሉን ነገር ይወርሳሉ፣ እግዚሐብሔር ከእነርሱ ጋር ይኖራል፣ እነሱም ልጆች ይሆኑታል። (ራዕይ 21፡ 7) ።
ስለዚህ ወደ ሙሉ ክብ መጣን ማለት ነው። እግዚሐብሔር ከእርሱ ጋር ህብረት እንድናደርግ ፈጠረን። የሰው ልጅ ኃጢያት በመስራቱ ህብረቱ እንዲቋረጥ አደረገ። እግዚሐብሔር ከመረጣቸው ጋር ህብረቱን እንደገና በማደስ በላይኛው ቤት ከእርሱ ጋር እንዲኖሩ ያደርጋል። በሕይወት ዑደት ውስጥ ብዙ ነገር ካሳኩ በኋላ ለዘላለሙ ከእግዚሐብሔር ጋር መለያየት ከውድቀት ሁሉ የከፋው ነው። ነገር ግን እግዚሐብሔር ዘላለማዊ ደስታ ዕውን የሚሆንበትን መንገድ ከመቀየሱም ባሻገር(ሉቃስ 23፡ 43) በምድርም ላይ ሕይወት አርኪና ትርጉም ያለው እንዲሆን ሁኔታዎችን አመቻችቶአል። እንዴት ነው ይህ ዘላለማዊ ደስታና “ገነት በምድር” የሚገኘው?
ብዙ ግቦች ባዶነታቸው የሚረጋገጠው እነሱን ለማከናወን በርካታ ዓመታት ካለፈ በኋላ ነው። በኛ ሰብዓዊ ሕብረተሰብ ትርጉም እናገኛለን ብለው በማሰብ ብዙ ሰዎች በርካታ ዓላማዎችን ያራምዳሉ። ከነዚህም የሕይወት ዓላማዎች የንግድ ስኬት፣ ሐብት፣ መልካም ግንኙነት፣ ወሲብ፣ መዝናናትና ለሌሎች ሰዎች ጥሩ ነገር መስራትን ያካትታሉ። ሰዎች ሲመሰክሩ እንደተስተዋለው ሐብት የማከማቸት፣ መልካም ግንኙነት የመመስረትና ደስታን የማግኘት ዓላማቸውን ቢያሳኩም ማንም ሊሞላው የማይችል ባዶነት እንደሚሰማቸው ተናግረዋል።
የመፅሐፈ መክብብ ፀሐፊ ይህንን ስሜት ለመግለፅ “ከንቱ!...የከንቱ ከንቱ! ሁሉ ከንቱ ነው” ይላል(መፅሐፈ መክብብ 1፡2)። የመፅሐፈ መክብብ ፀሐፊ የሆነው ንጉሥ ሰለሞን ከልክ በላይ የሆነ ሐብት፣ በእርሱ ዘመንና በኛ ጊዜ ከነበረ ማንም ሰው የሚበልጥ ጥበብ፣ በብዙ መቶ የሚቆጠሩ ዕቁባቶች፣ መንግስታት የሚቀኑበት ቤተመንግስትና የአትክልት ስፍራ፣ ምርጥ የሆነ ምግብ፣ ወይንጠጅና አለየተባለ መደሰቻና መዝናኛ ነበረው። ጠቢቡ አንድ ጊዜ ሲናገር ልቡ የተመኘውን ያሳድድ ነበር። በዓይኖቻችን የምናየውና በስሜቶቻችን የምናጣጥመው ኑሮ ብለን የምንኖረው “ከፀሐይ በታች ያለው ሕይወት” ከንቱ ነው ሲል አጣጥሎታል።
ይህ ባዶነት ለምን ተከሰተ? ምክንያቱም እግዚሐብሔር የፈጠረን የዚህና አሁን ከምንለማመደው ባሻገር ላለው ነገር ነው። ሠለሞን ስለእግዚሐብሔር ሲናገር “ሰው መርምሮ እንዳያገኝ ዘላለምነትን በልቡ ሰጠው” ብሏል። (መፅሐፈ መክብብ 3፡11)። ሁላችንም በልባችን እንደምናውቀው ያለው ነገር “እዚህና አሁን” ያለው ብቻ እንዳልሆነ እንገነዘባለን። የመፅሐፍ ቅዱስ የመጀመሪያ መፅሐፍ በሆነው በዘፍጥረት ውስጥ እግዚሐብሔር የሰው ልጅን በራሱ መልክ እንደሰራው እናነባለን። (ዘፍጥረት 1፡26)። እኛ ከሌላ ነገር (ከሌላ የሕይወት ቅርፅ) ይልቅ አፈጣጠራችን ወደ እግዚሐብሔር የቀረበ እንደሆነ የሚያሳየን ነው። ከዚህም በተጨማሪ የምናገኘው ነገር የሰው ልጅ በኃጢት ወድቆ የኃጢያት መርገም በምድር ላይ ከመምጣቱ በፊት የሚከተሉት ነገሮች ተግባራዊ ሆነዋል። (1) እግዚሐብሔር ሰውን ማህበራዊ ፍጡር አድርጎ አበጀው።(ዘፍጥረት 2፡ 18-25)፣ (2) እግዚሐብሔር ለሰው ልጅ ሥራ ሰጠው። (ዘፍጥረት 2፡ 15)፣ (3)እግዚሐብሔር ከሰው ጋር ህብረት ነበረው። (ዘፍጥረት 3፡ 8) እና (4) ሰው ምድርን እንዲገዛ እግዚሐብሔር ሥልጣን ሰጠው። (ዘፍጥረት 1፡ 26)። የእነዚህ ነገሮች ትርጉም ምንድ ነው? እነዚህ እያንዳንዱ ለሕይወታችን እርካታ እንዲያስገኙልን ነው። እግዚሐብሔር አቅዶ የነበረው፣ ነገር ግን እነዚህ ሁሉ (በተለይም ሰው ከእግዚሐብሔር ጋር ያለው ህብረት) ተለዋውጠዋል። ምክንያቱም የሰው ልጅ በኃጢያት ከወደቀ በኋላ እርግማን በምድር ላይ ተግባራዊ በመሆኑ ነው። (ዘፍጥረት 3)።
የመፅሐፍ ቅዱስ የመጨረሻ ክፍል በሆነው በራዕይ መፅሐፍ እግዚሐብሔር አንድ ነገር አስቀምጧል። አሁን በተጨማጭ የምናውቃቸውን ምድርና ሰማይን አስወግዶ አዲስ ምድርና ሰማይን በመፍጠር ዘላለማዊ ሕይወትን ይተካል። በዚያን ጊዜ ከዳነው የሰው ልጅ ጋር ሙሉ ህብረት ያደርጋል። ያልዳኑትን ይፈርድባቸውና እርባናየለሽ ተብለው ወደ እሳትባህር ይጣላሉ። (ራዕይ 20፡ 11-15)። የኃጢያት መርገም ይወገዳል። ከዚህ በኋላ ኃጢያት፣ ሐዘን፣ በሽታ፣ ሞትና ስቃይ ከቶ አይኖርም።( ራዕይ 21፡ 4)። አማኞችም ሁሉን ነገር ይወርሳሉ፣ እግዚሐብሔር ከእነርሱ ጋር ይኖራል፣ እነሱም ልጆች ይሆኑታል። (ራዕይ 21፡ 7) ።
ስለዚህ ወደ ሙሉ ክብ መጣን ማለት ነው። እግዚሐብሔር ከእርሱ ጋር ህብረት እንድናደርግ ፈጠረን። የሰው ልጅ ኃጢያት በመስራቱ ህብረቱ እንዲቋረጥ አደረገ። እግዚሐብሔር ከመረጣቸው ጋር ህብረቱን እንደገና በማደስ በላይኛው ቤት ከእርሱ ጋር እንዲኖሩ ያደርጋል። በሕይወት ዑደት ውስጥ ብዙ ነገር ካሳኩ በኋላ ለዘላለሙ ከእግዚሐብሔር ጋር መለያየት ከውድቀት ሁሉ የከፋው ነው። ነገር ግን እግዚሐብሔር ዘላለማዊ ደስታ ዕውን የሚሆንበትን መንገድ ከመቀየሱም ባሻገር(ሉቃስ 23፡ 43) በምድርም ላይ ሕይወት አርኪና ትርጉም ያለው እንዲሆን ሁኔታዎችን አመቻችቶአል። እንዴት ነው ይህ ዘላለማዊ ደስታና “ገነት በምድር” የሚገኘው?
No comments:
Post a Comment